| |

South Link Connections Metro በደቡብ ኪንግ ካውንቲ የመጨረሻሻ የጉዞ መስመር ማሻሻያ ያቀርባል

የSouth Link Connections ፎቶ - የጉዞ መስመር 193 እስከ Federal Way መሻገሪያ ማእከል

ይህ የብሎግ ልጥፍ በእነዚ ቋንቋዎች ይገኛል፡ English (እንግሊዝኛ) العربية (አረብኛ) 简体中文 (ቀላል ቻይንኛ) 繁體中文 (ባህላዊ ቻይንኛ) دری (ዳሪ) Français (French) 한국어 (ኮሪያኛ) Русский (ራሺያኛ) Af Soomaali (ሶማሊ) Español (ስፓንኛ) Tagalog ( ታንጋሎግ) ትግርኛ Українська (ዩክሬንያን) Tiếng Việt (ቪትናሜሴ)

የLink ቀላል ባቡር በKent/Des Moines፣ Star Lake እና በFederal Way ማሀል ከተማ ሶስት አዳዲስ ጣብያዎች በመጨመር ወደ ደቡብ ተዘርግቷል። Metro የደቡብ ኪንግ ካውንቲ ማሕበረሰብ የመጓጓዧ አማራጮችን ለማሻሻል ከSound Transit እና ሌሎች አጋሮች ጋስ መስራቱን ቀጥሏል።

South Link Connections ፕሮጀክት፣ የMetro አውቶብሶች ከLink ቀላል ባቡር፣ የST Express አውቶብሶች እና በኪንግ ካውንቲ ያሉ የPierce Transit አገልግሎቶች ጋር በማስተሳሰር አዲስ የመሸጋገሪያ ኔትወርክ ይፈጥራል።

ከማህበረሰብ አባላት እና አጋሮቻችን አስተያየት ከሰማን በኋላ፣ Metro የመጨረሻውን የመሸጋገሪያ ኔትወርክ ፕሮፖዛላችን በማካፈል ጓግተዋል። እነዚህ፣ ከነዋሪዎች እና ከAlgona፣ Auburn፣ Burien፣ Des Moines፣ Federal Way፣ Kent፣ Normandy Park፣ Pacific፣ SeaTac፣ Tukwila እና ያልተመዘገቡ የኪንግ ካውንቲ አከባቢዎች ባለ ስልጣናት ጋር በመተባበር የተሰሩ ነው።

የፕሮጀክት ተንቀሳቃሽነት ቅድሚያዎች

በመላው ፕሮጀክት፣ Metro በአካል ከሚደረግ ተሳትፎ፣ የበይነ መረብ ዳሰሳ ጥናት፣ ከማህበረሰብ ተኮር ድርጅቶች ጋር በጋራ በመስራት፣ እንዲሁም ከSouth Link እንቅስቃሴ እና የአጋር ግምገማ ቦርዶች የምክክር ውይይቶች በኩል የማህበረሰብ አስተያየት ሰብስቧል። በመጀመሪያው የህዝብ ተሳትፎ ምዕራፍ፣ Metro ከእንቅስቃሴ ቦርድ ጋር በመስራት አምስት ዋና ዋና የእንቅስቃሴ ቅድሚያዎችን ከዚህ በታች አስቀምጧል። Metro እነዚህን ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የመሸጋገሪያ ኔትወርክ ለውጦችን ለማሳወቅ ተጠቅሟል።

የተሻለ መሻገሪያ ሽፋን

የተሻሻለ የጠዋት እና የሌሊት አገልግሎት

በፕሮጀክት አካባቢ ውስጥ እና ከዚያም በላይ ፈጣን የጉዞ ጊዜ

የተሻሻለ የምስራቅ-ምዕራብ የትራንዚት ግንኙነቶች

ተጨማሪ የሳምንት መጨረሻ አገልግሎት፣ በተለይም በቅዳሜዎች

የመጨረሻው የአውታረ መረብ ፕሮፖዛል ዋና ዋና ነጥቦች

  • አዲስ ህዝብ መጓጓዣ ግንኙነቶች፦ ወደ Link ቀላል ባቡር ጣቢያዎች አዲስ እና የተሻሻሉ ግንኙነቶችን ያክላል።
  • ተጨማሪ የሙሉ ቀን አገልግሎት፦ ተጨማሪ የሙሉ ቀን አገልግሎት፦ ቀኑን ሙሉ፣ በየቀኑ በሚሰሩ የአውቶቡስ መስመሮች ላይ ኢንቨስት ያደርጋል። በሳምንቱ ቀናት 51% ተጨማሪ ጉዞዎች እና ቅዳሜና እሁድ 72% ተጨማሪ ጉዞዎች ይኖራሉ።
  • የተስፋፋ የሳምንት መጨረሻ አገልግሎት፦ አዲስ የቅዳሜ እና የእሁድ አገልግሎትን ያስተዋውቃል እና በዋና ዋና መንገዶች ላይ የሳምንቱ መጨረሻ ድግግሞሽን ይጨምራል። በተለይም፣ በ Burien አዲስ የሳምንት መጨረሻ አገልግሎት፣ በKent እና Federal Way መካከል አዲስ የእሁድ አገልግሎት እና በKent Des Moines ጣቢያ ጣቢያ፣ Kent ጣቢያ፣ Kent East Hill እና Green River College መካከል በተደጋጋሚ የሳምንት መጨረሻ አገልግሎት ይኖራል። የመጨረሻው የአውታረ መረብ ፕሮፖዛል ቅዳሜ ዕለት 57% ተጨማሪ ጉዞዎችን እና እሁድ ዕለት ደግሞ ከዛሬው ጋር ሲነጻጸር በእጥፍ የሚበልጥ ጉዞዎችን ያቀርባል።
  • Stronger east–west travel: Improves essential east-west routes connecting major destinations across the area including:
    • Highline College፣ Kent ጣቢያ እና Green River College
    • የTwin Lakes Park & Ride፣ የFederal Way Downtown ጣቢያ እና Auburn ጣቢያ
  • አዲስ በፍላጎት ላይ ያሉ አማራጮች፦ በ Federal Way እና Auburnውስጥ ሁለት አዳዲስ የMetro Flex በፍላጎት ላይ ፓይለት አገልግሎቶችን አስጀምሯል።
  • ፈጣን አገልግሎት፦ ይህንን ግንኙነት ፈጣን፣ ቀጥተኛ እና ለማሰስ ቀላል ለማድረግ በwest Federal Way እና በdowntown Federal Way መካከል ያሉትን የአውቶቡስ መስመሮች ያዘምናል።
  • ቀላል አውታረ መረብ፦ አሁን በየLink ቀላል ባቡር የሚሸፈነውን አገልግሎት ለመቀነስ እና ህዝብ መጓጓዣ ሰዓቶችን በጣም በሚያስፈልጉበት ቦታ እንደገና ኢንቨስት ለማድረግ፣ የሚከተሉትን ለማስወገድ ሀሳብ አቅርበናል፦ 122*፣ 123*፣ 154*፣ 157*፣ 162፣ 165 (ሙሉ በሙሉ በአውራ መስመሮች ተተክቷል 164/166)፣ 177፣ 178*፣ 179*፣ 190*፣ 197*፣ DART 901። በተጨማሪም፣ መስመሮች 193 ለጉዞ ቅነሳ ታቅዷል፣ አንድ ጥዋት ያነሰ እና አንድ ከሰአት ባነሰ ጉዞ።

*በአሁኑ ጊዜ የተቋረጡ/ያልተሰሩ መስመሮች።

ቀጣይ እርምጃዎች

የየኪንግ ካውንቲ ኤክሰኪዩቲቭ ለታቀደው South Link Connections የኔትወርክ ኢንቨስትመንቶች ከግምት ውስጥ ለማስገባት እና ድምጽ ለመስጠት የመጨረሻውን የደንብ ጥቅል ወደ ኪንግ ካውንቲ ምክር ቤት አስገብቷል። የኪንግ ካውንቲ ስራ አስፈ ካውንስል ሃሳቡን በዚህ የጸደይ ወቅት ለማየት ቀጠሮ ተዘዋል።

የአገልግሎት ለውጥ ትግበራ

Metro በዓመት ሁለቴ፣ ማለትም ጸደይ እና መኸር ላይ ትላልቅ ለውጦች ይተገብራል። Federal Way Link Extension ታህሳስ 2025 ስለተከፈተ፣ Metro ለፀደይ 2026 የአገልግሎት ለውጥ መጋቢት 28 ከSouth Link Connections የመጨረሻ የኔትወርክ ፕሮፖዛል ጋር የተጣጣሙ ጥቃቅን የአገልግሎት ለውጦች ለማድረግ እያቀደ ነው። እነዚህ ለውጦች የሚያተኩሩት መንገዶችን ወደ አዲስ ጣቢያዎች በማገናኘት እና የአገልግሎት ሰአቶችን በማስፋት ላይ ነው።

ኪንግ ካውንቲ ምክር ቤት ካጸደቀው፣ የቀሩት የታቀዱ ለውጦች ተግባራዊ ማድረግ የሚጀመረው በጸደይ 2026 የአገልግሎት ለውጥ ነው። በእያንዳንዱ የMetro የአገልግሎት ለውጥ ትግበራ፣ አገልግሎቱ በአስተማማኝ ሁኔታ መሰጠቱን ለማረጋገጥ በሰው ሃይል አቅም ላይ የተመሰረተ ነው፤ ይህም ለውጦች በደረጃ ሊሆን ይችላል። ልዩ ለውጦች መቼ እንደሚሆኑ የበለጠ መረጃ ለማግኘት፣ የMetro የአገልግሎት ለውጥ ገጽን ይጎብኙ። የአገልግሎት ለውጦች Metro Matters ብሎግ ላይም ይለጠፋሉ።

ያነጋግሩን

እባክዎ ከታች ባለው ኢሜይል በኩል አድርገው በመረጡት ቋንቋ ያግኙን፦ haveasay@kingcounty.gov

have a say logo

አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት ለደንበኝነት ይመዝገቡ

የፕሮጀክት ዝመናዎችን እንዲሁም ስለ ስለክስተቶች እና ወሳኝ ጅማሬዎች ማስታወቂያዎች ለማግኘት በፕሮጀክት ጋዜጣችን ይመዝገቡ። ስለዚህ አገልግሎት ማንኛውም ጥያቄ ካሎት እባክዎ ያነጋግሩን።

ምላሾትን ያስቀምጡ